"ሕዝቤና አገሬ በነፃ እንዳስተማሩኝ ሁሉ፤ እኔም አንድ የሥነ ስዕል ማዕከል ከፍቼ ወገኖቼን በነፃ ለማስተማር ውጥን አለኝ" አርቲስት ወርቅነህ በዙ

Woman II.jpg

'Dream of Saints' by Artist Workneh Bezu. Credit: Workneh Bezu

ሰዓሊ ወርቅነህ በዙ "ስኬታማ ነኝ ብዬ አስባለሁ" ይላል። በኢትዮጵያ የሥነ ስዕል ዓለም ውስጥ የበኩሉን ምን ዓይነት የሥነ ጥበብ አስተዋፅዖዎችን እንዳበረከተና ሰሞኑን ዩኔስኮ ኒው ዮርክ ላይ ባሰናዳው ሲምፖዚየም ስላቀረባቸው የጥበብ ሥራዎቹና ስለተበረከተለት ሽልማት ይገልጣል።


ስኬት

ሰዓሊ ወርቅነህ በዙ፤ በሥነ ጥበቡ ሕይወት ስኬታማ መሆኑን ይገልጣል።

ያም ሊሆን የቻለው "በትክክል የሚያስተምሩ መምህራኖችን ማግኘቴና በትክክል ጥበበን መግለፅ መቻሌ የመጀመሪያው ሲሆን፤ ሁለተኛው ላለፉት 20 ዓመታት የሙሉ ጊዜ አርቲስት ሆኔ መሥራት መቻሌ ነው" ሲል ያስረዳል።

ይህም "ጥበቡን አንድ ከፍ ያለ ደረጃ ላይ አድርሽያለሁ ማለት ነው" ሲልም የጥበብ በረከት አስተዋፅዖ እሳቤውን አመላክቷል።
Drean of Saints Woman .jpg
'Dream of Saints' by Artist Workneh Bezu. Credit: Workneh Bezu
ወርቅነህ ብዙዎቹ በአገር ውስጥና በባሕር ማዶ የተወደዱለት ሥራዎቹ ከአማልክት ጋር የተያያዙ ናቸው።
Angel.jpg
Credit: Workbeh Bezu
ሰዓሊ ወርቅነህ የሥነ ስዕል ሥራዎቹን በማሊ፣ ግብፅ፣ ዩናይትድ ስቴትስ፣ ስዊትዘርላንድና ፊንላንድ አቅርቧል።

ሰሞኑንም በኒው ዮርክ በተዘጋጀ ሲምፖዚየም የጥበብ ሥራዎችን አቅርቧል።

ሽልማትም አግኝቶበታል።
WORKNEH BEZU NY.jpg
Credit: W.Bezu
ውጥኖች

ከቅርብ ጊዜ የወርቅነህ ውጥኖች አንዱ የስዕል ሥራዎቹን ፖርቱጋል ውስጥ ላለ አንድ ስቱዲዮ ለማቅረብ ስምምነት ላይ መድረሱ ነው።

የረጅም ጊዜ ትልሞቹ አንድ የግል ጋለሪ ማቋቋምና ታዳጊ የጥበብ ሰዎች ሕዝብና አገር ከቸሩት ትሩፋት ማጋራት ነው።
woman in green.jpg
Credit: Workneh Bezu

Share